Quantcast
Channel: አስተያየት
Viewing all articles
Browse latest Browse all 720

አዲስ አበባ ሁለተኛውን የሒልተን ሆቴል ልታገኝ ነው

$
0
0

ታፍቢቢ ቢዝነስ ኃላፊነቱ የተወሰነ የግል ማኅበር ከሒልተን ዓለም አቀፍ ግሩፕ ጋር በመስማማት ‹‹ደብልትሪ ባይ ሒልተን›› የተባለውን የሆቴል ብራንድ በኢትዮጵያ ለማስተዳደር ስምምነት ተፈራረሙ፡፡

በሒልተን በዓለም አቀፍ ሥር ከሚተዳደሩ 15 ታዋቂ ብራንዶች መካከል አንዱ የሆነው ደብልትሪ ባይ ሒልተን በሚፈቅደው ከፍተኛ ደረጃ በአዲስ አበባ ቦሌ ዓለም አቀፍ ኤርፖርት አካባቢ፣ ብራስ ሆስፒታል አጠገብ እየተገነባ የሚገኘው ይህ ሆቴል፣ ሒልተን እንዲያስተዳድረው ስምምነት የተደረገው ሰኞ፣ ነሐሴ 29 ቀን 2009 ዓ.ም. ነበር፡፡ ይህን ሆቴል ሒልተን እንዲያስረዳድረው ስምምነት የተደረገው ሰኞ፣ ነሐሴ 29 ቀን 2009 ዓ.ም ነበር፡፡ ይህን ሆቴል ሒልተን እንዲያስተዳድረው ለማድረግ የተደረገው ድርድር ረዘም ያለ ጊዜ መውሰዱም ታውቋል፡፡

በግንባታ ላይ የሚገኘው ባለ 11 ፎቅ ሆቴል፣ በአሁኑ ጊዜ 70 በመቶ የግንባታ ሒደቱ መጠናቀቁን የታፍቢቢ ቢዝነስ ግሩፕ ማኔጂንግ ዳይሬክተር አቶ ተካ አስፋው ገልጸዋል፡፡

ሆቴሉ አውሮፓ ሠራሽ በሆኑ የግንባታ ዕቃዎች እየተገነባ እንደሚገኝ ሲታወቅ፣ ከቦሌ ኤርፖርት በአንድ ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ መገኘቱና በአዲስ አበባ ከተማ ዋና እምብርት አካባቢ ላይ መገንባቱ፣ ከኤርፖርት በቅርብ ርቀት መቆየት ለሚመርጡ እንግዶች ተፈላጊ እንደሚያደርገውም ኃላፊዎቹ ይገልጻሉ፡፡

የሆቴሉ የ30 በመቶ ቀሪዎቹ ግንባታዎች በስምንት ወራት ውስጥ ተጠናቀው ሆቴሉ አገልግሎት መስጠት እንደሚጀመር አቶ ተካ ገልጸዋል፡፡ ለሆቴሉ ውጫዊ ግንባታ፣ ውስጣዊ ዲዛይንና ልዩ ልዩ መገልገያ ዕቃዎችን ለማሟላት እስከ 300 ሚሊዮን ብር ድረስ እንደሚጠይቅ ተገምቷል፡፡ በግንባታው ሒደት ከ500 ሰዎች በላይ የተሳተፉ ሲሆን፣ አጠቃላይ ግንባታው ተጠናቆ ወደ ሥራ ሲገባም ከ400 እስከ 500 ሰዎች የሥራ ዕድል ሊፈጥር እንደሚችል አቶ ተካ ገልጸዋል፡፡

በዓለም ስመ ጥር የሆኑ የሥነ ሕንፃ ኩባንያዎችን በማወዳደር የሆቴል ዲዛይን እንዲሠራ የተመረጠው ኩባንያ ባቀረበው ዲዛይን መሠረት የሆቴሉ ግንባታ መጀመሩንም አቶ ተካ ገልጸዋል፡፡ ‹‹ሆቴላችን በዓለም ካሉ ታዋቂ ሆቴሎች መካከል አንዱ እንዲሆን በነበረን ምኞትና ጥረት፣ አንጋፋና በዓለም ታዋቂነትን ካተረፉት ውስጥ ሒልተን ሆቴልን በመምረጥ ለረዥም ጊዜ በመወያየትና ግንኙነት በማድረግ ዛሬ የተፈራረምነው ስምምነት ላይ ደርሰናል፡፡ በዚህ መሠረት ከሒልተን ዓለም አቀፍ ሆቴሎች አንዱና ታዋቂ የሆነውን ‹‹ደብልትሪ›› ብራንድን መርጠናል፤›› ብለዋል፡፡

በደብልትሪ ባይ ሒልተን ብራንዱን በ40 አገሮች ውስጥ 500 ሆቴሎችን የሚያስተዳድረው ሒልተን ዓለም አቀፍ፣ በሥሩ ከሚገኙ 15ቱ ብራንዶች ውስጥ በኢትዮጵያ አዲስ አበባ ሒልተንና በሐዋሳ በሰንሻይን ኢንቨስትመንት ግሩፕ እየገነባው የሚገኘው ሆቴል ይጠቀሳሉ፡፡

ሒልተን ሆቴል በአዲስ አበባ ሲያስተዳድረው የቆየው ንብረት ከ50 ዓመታት በላይ በማስቆጠር በዓለም አቀፍ ደረጃ ከሚታወቁ ብራንድ ሆቴሎች ፈር ቀዳጁ ነው፡፡ ይህንኑ በማስታወስ፣ አዲሱን ሆቴል ለማስተዳደር የተስማማው ሒልተን በአፍሪካም ሆነ በዓለም በርካታ መዳረሻዎች ካሉት የኢትዮጵያ አየር መንገድ መሥሪያ ቤት አቅራቢያ መገንባቱም አዲሱን ሆቴል ተመራጭ ከሚያደርጉት መካከል እንደሚመደብ፣ የሒልተን ሆቴል የአውሮፓ፣ መካከለኛው ምሥራቅና አፍሪካ ከፍተኛ ምክትል ፕሬዚዳንት ፓትሪክ ፊትዝጊበን ተናግረዋል፡፡ በርካታ ትዕይቶች ከሚታደሙበት ከሚሊኒየም አዳራሽ ጀምሮ፣ ለአፍሪካ ኢኮኖሚክ ኮሚሽን፣ ለአፍሪካ ኅብረትና ለሌሎችም ትልልቅ ተቋማት አማካይ ቦታ ላይ የሚገኝ፣ ከፍተኛ በሚባሉት የሆቴል ደረጃዎች መስክ የሚመደበው ይህ ሆቴል ለኢትዮጵያ የሆቴል ኢንዱስትሪ ትልቅ እሴት እንደሚሆንም ጠቅሰዋል፡፡

 

Standard (Image)

Viewing all articles
Browse latest Browse all 720

Trending Articles