Quantcast
Channel: አስተያየት
Viewing all articles
Browse latest Browse all 720

ለእህል ጥራት ተስፋ የሚደረገው ከረጢት የድኅረ ብክለትን ለመቀነስ እያገዘ ነው

$
0
0

በድኅረ ምርት ከአሥር እስከ 12 በመቶ የሚሆነውን ብክነት ለመቀነስ የሚያግዝ የእህል ማከማቻ ቀረጢት ለአርሶ አደሮች መቅረብ ጀመረ፡፡

ሔርሜቲክ በተሰኘ ቴክኖሎጂ (አየር ወደ ከረጢት ውስጥ እንዳይገባ የሚያግድ) አማካይነት የሚሠራው ቀረጢት፣ የትኛውም የእህል ምርት ከነበረበት የጥራት ደረጃ ሳይጓደልና ሳይበላሽ ለሁለት ዓመታት እንዲቆይ የሚያስችል መሆኑን ቴክኖሎጂውን እያቀረበ የሚገኘው የሻያሾኔ ኃላፊነቱ የተወሰነ የግል ማኅበር ዋና ሥራ አስኪያጅ አቶ ያሬድ ሠርፀ ይናገራሉ፡፡

የግብርና ማማከር፣ የግብርና ቴክኖሎጂዎችን የማስፋፋትና የማስተዋወቅ ሥራ የሚሠራው ድርጅቱ፣ ቴክኖሎጂውን የሚያስመርተው ከሦስት ፋብሪካዎች ጋር በመተባበር  ነው፡፡ በኢትዮጵያ በ27 ዞኖች ውስጥ ለሚገኙ 6,000 መንደሮች ምርቱን ለማሰራጨት የማስተዋወቅ ሥራ መካሔዱን የሚናገሩት አቶ ያሬድ፣ ባለፉት ሦስት ዓመታት 280,000 ከረጢቶችን ማሠራጨት እንደተቻለም ገልጸዋል፡፡ በመጪው ዓመት  360,000 ቀረጢቶችን ለአርሶ አደሩ የማሠራጨት ዕቅድ እንደተያዘም አስታውቀዋል፡፡

ቴክኖሎጂው ከተሠራጨባቸው የአገሪቱ ክፍሎች መካከል የመራቤቴ ወረዳ አንዱ ሲሆን፣ እሑድ፣ ነሐሴ 27 ቀን 2009 ዓ.ም.  ለወደራ ኅብረት ሥራ ዩኒየን አባል አርሶ አደሮች ቴክኖሎጂውን ለማስተዋወቅ ተሞክሯል፡፡

የኔዘርላንድስ መንግሥት የልማት ድርጅት ድጋፍ በሚሰጠው ማኅበራት ለለውጥ በተሰኘ ፕሮጀክት አማይነት፣ ቴክኖሎጂው በኦሮሚያ፣ በአማራና በደቡብ ክልሎች ለሚገኙ አርሶ አደሮች ለማዳረስ እንቅስቃሴ እየተደረገ ይገኛል፡፡ በድርጅቱ የአግሪ ቢዝነስ አማካሪ አቶ መስፍን ወልደሥላሴ እንደጠቀሱት፣ መራቤቴን ጨምሮ በሦስቱ ክልሎች ውስጥ በሚገኙ ሦስት ዩኒየኖች አማካይነት 4,500 ቀረጢት መሰራጨቱም ታውቋል፡፡ በሚቀጥሉት ወራት 6,000 ከረጢቶችን ለማሰራጨት እንቅስቃሴ እንደሚደረግ ተናግረዋል፡፡

የአንዱ ከረጢት ዋጋ ከ70 እስከ 100 ብር ሲሆን፣ ፕሮጀክቱ ተግባራዊ በሚደረግባቸው የአገሪቱ ክፍሎች ለሚገኙ አርሶ አደሮች 47 ብር በመክፈል ቀረጢቱን እንዲያገኙ ድጋፍ እየተደረገ መሆኑም ተጠቅሷል፡፡ ‹‹280,000 ማሠራጨት ብዙ የሚባል አይደለም፡፡ ነገር ግን እያደገ የመጣበት ፍጥነት ከፍተኛ ነው፡፡ ቴክኖሎጂው ከተዋወቀ ወዲህ ሥርጭቱ በሁለትና በሦስት እጥፍ እያደገ ነው፤›› በማለት የገለጹት አቶ ያሬድ፣ ምርቱን በሁሉም የአገሪቱ ክፍሎች ለማድረስ የአቅም ችግር ባይኖርባም የጥሬ ዕቃ አቅርቦት ችግር ግን ፈተና እንደሆነ ይናገራሉ፡፡

ቴክኖሎጂውን የሚያከፋፍሉ ለአርሶ አደሩ በቅርብ የሚገኙ ወኪሎች አለመኖራቸው የዋጋ ውድነት እንዲፈጠር እንዳደረገና ይህንን አርሶ አደሮች በተደጋጋሚ ጊዜ የሚነሱት ጥያቄ እንደሆነ ተጠቅሷል፡፡ ከረጢቱን በመጠቀም ምርት ሳይበላሽ ማትረፍ ከሚችሉት መጠን አኳያ ሲታይ፣ ዋጋው እዚህ ግባ የሚባል አይደለም የሚሉት አቶ ያሬድ፣ የምርት መጠኑ ሲጨምር የአንዱ ፕላስቲክ ዋጋ ከሁለት እስከ ሦስት ብር ድረስ የዋጋ ቅናሽ ሊያሳይ እንደሚችል ይናገራሉ፡፡

መንግሥት ትኩረት የሚሰጠው ከሆነና የቀረጥ አከፋፈል ሥርዓቱን የሚያሻሽለው ከሆነም አሁን ካለው በታች በቅናሽ ሊሠራጭ እንደሚችል አክለዋል፡፡  የድኅረ ምርት ብክነት በአገሪቱ ትልቅ ችግር ሆኖ ቆይቷል፡፡ ከአሥር እስከ 12 በመቶ የሚሆነው የምርት ብክነትም ምርት በማከማቸት ወቅት የሚከሰት ነው፡፡ ሆኖም ግን በድኅረ ምርት አሰባሰብ የሚታየው አማካይ የአገሪቱ የምርት ብክነት እስከ 30 በመቶ እንደሚገመት መረጃዎች ያሳያሉ፡፡ ምርት በነቀዝ፣ በአይጥና በተለያዩ ተባዮች ስለሚበላ፣ በጥራትም ሆነ በመጠን ሲቀንስ ይታያል፡፡ በተለይ ሞቃታማ በሆኑ የአገሪቱ ክፍሎች የግብርና ምርቶች በከፍተኛ ደረጃ በተባይ ለሚከሰት ብልሽት የተጋለጡ ናቸው፡፡

የወደራ ሁለገብ የገበሬዎች ኅብረት ሥራ ማኅበራት ዩኒየን ሥራ አስኪያጅ አቶ ይርዳው ዓለሙ እንደሚሉት፣ በአካባቢ የሚገኙ አርሶ አደሮች ምርታቸውን ከማሳ ከሰበሰቡ በኋላ ሳይበላሽ አከማችተው ለማቆየት ሲቸገሩ ቆይተዋል፡፡ ከሁለት ወራት በላይ ማስቀመጥ እንደማይችሉም ገልጸዋል፡፡

ማሽላ፣ በቆሎና ባቄላ በተለየ ሁኔታ በነቀዝ የሚጠቁ የምርት ዓይነቶች ሲሆኑ፣  አርሶ አደሮች ተስማሚ የማከማቻ ዘዴዎችን በማጣት፣ ዋጋውን በግማሽ ቀንሶ ለገበያ ለማቅረብ እንደሚገደዱ ይናገራሉ፡፡ የኢትዮጵየ ምርት ገበያ አባል የሆነው ይህ ዩኒየን፣ በአካባቢው የሚመረቱ የተለያዩ ጥራጥሬዎችና የሰብል እህሎችን ወደ ውጭ ለመላክ እየተንቀሳቀሰ ይገኛል፡፡ ይሁንና ባለፈው ዓመት 400 ኩንታል የማሾና ሌሎች ጥራጥሬዎችን ለውጭ ገበያ ቢያቀርቡም፣ በጥራት ጉድለት ምክንያት ምርቱ  እንደተመለሰባቸው አስታውሰዋል፡፡ በመሆኑም አዲሱን ቀረጢት ከእንዲህ ዓይነቱ ሥጋት እንደሚቀረፍ ተስፋ ያደርጉበታል፡፡  

 

Standard (Image)

Viewing all articles
Browse latest Browse all 720

Trending Articles