Quantcast
Channel: አስተያየት
Viewing all articles
Browse latest Browse all 720

እያገገመ ከሚገኘው ቱሪዝም ዘርፍ የ2.6 ቢሊዮን ዶላር ገቢ ተገኘ

$
0
0

 

  • በዓመቱ የ3.7 ቢሊዮን ዶላር ገቢ ይጠበቅበታል

በአገሪቱ በተከሰተው ፖለቲካዊ ትኩሳት ምክንያት በውጭ ጎብኝዎች መቀነስ ችግር ውስጥ የገባው የቱሪዝም ዘርፍ፣ በማገገም ላይ እንደሚገኝና በሦስተኛው ሩብ ዓመት የተመዘገበው የቱሪስት ፍሰት ከቀደሙት ስድስት ወራት አኳያ ጭማሪ እንዳሳየ የባህልና ቱሪዝም ሚኒስቴር አስታወቀ፡፡

የሚኒስቴሩ የሕዝብ ግንኙነት ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር አቶ ገዛኸኝ አባተ የዘጠኝ ወራት አፈጻጸምን በማስመልከት ለጋዜጠኞች ይፋ ባደረጉት መረጃ መሠረት፣ በዘጠኝ ወራት ውስጥ የተመዘገበው የቱሪስቶች ቁጥር 686223 እንደሆነ ታውቋል፡፡ በሦስተኛው ሩብ ዓመት ብቻ የተመዘገው የቱሪስቶች ቁጥር 246869 ሲሆን፣ በመጀመሪያው ሩብ ዓመት 233032 እንዲሁም በሁለኛው ሩብ ዓመት 206327 ቱሪስቶች ወደ ኢትዮጵያ መምጣታቸው ተወስቷል፡፡

ምንም እንኳ የዘጠኝ ወራት አጠቃላይ የዘርፉ አፈጻጸም ከመጀሪያዎቹ ስድስት ወራት አኳያ ሲታይ ለውጥ አሳይቷል ቢባልም፣ ከዓምናው ተመሳሳይ የዘጠኝ ወራት ጊዜ ጋር ሲነጻጸር ግን ቀንሶ መገኘቱን አቶ ገዛኸኝ ይፋ አድርገዋል፡፡ በተለይም በመጀሪያዎቹ ሁለት የሩብ ዓመታት ወቅት ዘርፉ ከዜሮ በታች (-) 8.25 በመቶ ማስዝገቡ ሲጠቀስ፣ በሦስተኛው ሩብ ዓመት ግን ዕድገቱ ተሻሽሎ የ5.8 በመቶ ዕድገት ማሳየት እንደቻለ ተገልጿል፡፡ ይሁንና ካለፈው ዓመት ዘጠኝ ወራት አኳያ የ3.64 በመቶ ወይም የ25888 ጎብኝዎች ቅናሽ መመዝገቡን ለመረዳት ተችሏል፡፡

በአሁ ወቅት በየወሩ ከ76 ሺሕ በላይ ጎብኝዎች ወደ ኢትዮጵያ እንደሚመጡ ያመላከቱት አቶ ገዛኸኝ፣ በዚህ ዓመት የሚጠበቀው የቱሪስት ቁጥር አንድ ሚሊዮን ይደርሳል ተብሎ መታቀዱን አስታውሰዋል፡፡ ይሁንና ከመስከረም እስከ ጥር ባለው ጊዜ ውስጥ ከፍተኛው የጎብኚዎች ቁጥር የሚመዘገብበት ወቅት ሲሆን፣ በተለይ መጪው ጊዜ ክረምት እንደመሆኑ መጠን የታቀደውን መጠን ማሳካት መቻሉ አጠራጥሯል፡፡

ሚኒስቴሩ በሚከተለው ስሌት መሠረት አንድ ቱሪስት ወደ ኢትዮጵያ በሚመጣበት ወቅት በአማካይ 16 ቀናት ቆይታ በማድረግ በትንሹ 234 ዶላር ወጭ እንደሚያደርግ ይታሰባል፡፡ በዚህ ስሌት መሠረት እንዲሁም ወደ አንድ ሚሊዮን ቱሪስት (ለትራንዚት የሚመጣውን ጨምሮ፣ ለስብሰባና ለመዝናናት የሚመጡትን ያካትታል) እንደሚመጣ ታሳቢ በተደረገው መሠረት፣ በዓመቱ ሊገኝ የሚችለው ጠቅላላ የዘርፉ ገቢ ከ3.74 ቢሊዮን ዶላር በላይ እንደሚሆን ተገምቷል፡፡ ባለፈው ዓመት ከ800 ሺሕ በላይ ቱሪስቶች አገሪቱን ጎብኝተው ከ3.5 ቢሊዮን ዶላር ያላነሰ ገቢ መገኘቱ ይታወሳል፡፡

በአገሪቱ በተከሰቱ ፖለቲካዊ ቀውሶች ምክንያት ችግር የገጠመው ይህ ዘርፍ፣ በተለያዩ አገልግሎት መስጫ ተቋማትና በብሔራዊ ፓርኮች ላይ በደረሰው ጉዳት በተለይም አገሮች ባወጧቸው የጉዞ ክልከላዎችና ማሳሰቢያዎች ሳቢያ መቀዛቀዝ ሲያሳይ መቆየቱ ይጠቀሳል፡፡

የአዲስ አበባ ሆቴል ባለንብረቶች የዘርፍ ማኅበር በቅርቡ ይፋ ባደረገው መረጃ መሠረት በመጀመሪያው ሩብ ዓመት ብቻ በሆቴሎች የተለመደው የመኝታ ክፍሎች ይዞታ በአማካይ 67 በመቶ እንደነበር፣ ይሁንና በቀውሱ ሳቢያ የ20 በመቶ ቅናሽ መመዝገቡን ማኅበሩ አስታውቋል፡፡ ይኸው ቅናሽ እስከ ቅርብ ጊዜ ድረስ ባለበት መቀጠሉን የጠቀሰው ማኅበሩ፣ በዚህ ሳቢያም የ380 ሚሊዮን ብር ኪሣራ ሆቴሎች እንዳጋጠማቸውና መንግሥትም ይህንን ኪሳራቸውን የሚሸፍኑበት ወይም የሚያካክሱበት መፍትሔ እንዲፈልግላቸው እንደጠየቁ መዘገባችን አይዘነጋም፡፡

ርብርቦሽ ሲደረግ መቆየቱን፣ ዘርፉ በቀውስ ውስጥ እንደመሆኑ መጠን ቀውሱን የማብረድ ዕርምጃዎች ሲወሰዱ እንደነበር አቶ ገዛኸኝ ጠቅሰዋል፡፡ ምንም እንኳ የተወሰዱ ዕምጃዎችና ሲደረጉ የቆዩ እንቅስቃሴዎች ለውጥ አምጥተዋል ቢባልም የሚፈለገውን ያህል ለውጥ እንዳልመጣ ተናግረዋል፡፡

በቱሪዝም መስክ ከተወሰዱ ዕርምጃዎች መካከል ጠቅላይ ሚኒስትር ኃይለ ማርያም ደሳለኝ ያደረጓቸው ሹም ሽሮች ይጠቀሳሉ፡፡ በሚፈለገው ደረጃ ለውጥ አላመጡም የተባሉት የኢትዮጵያ ቱሪዝም ድርጅት እንዲሁም የኢትዮጵያ ብሔራዊ የዱር እንስሳት ጥበቃና ልማት ባለሥልጣን ኃላፊዎች ተነስተው በምትካቸው አዳዲስ ኃላፊዎች መተካታቸው ይታወሳል፡፡

 

Standard (Image)

Viewing all articles
Browse latest Browse all 720

Trending Articles