Quantcast
Channel: አስተያየት
Viewing all articles
Browse latest Browse all 720

በበልግ ወራት የዝናብ ሥርጭት መዳከሙ በድርቅ የተመቱ አካባቢዎችን የማገገም ዕድል አጥብቦታል ተባለ

$
0
0

 

  • በድጋሚ በተከሰተው ድርቅ ለ5.6 ሚሊዮን ዜጎች የሚያስፈልገው 948 ሚሊዮን ዶላር ዕርዳታ ማግኘት አልተቻለም

በባህር ሙቀት መጨመር ሳቢያ በተፈጠረው የአየር ፀባይ ለውጥ ሳቢያ ከ10.2 ሚሊዮን በላይ ዜጎች ለአስቸኳይ የምግብ ዕርዳታ ተዳርገው መቆየታቸው አይዘነጋም፡፡ ይህ ክስተት መቃለል በጀመረበት ወቅት የበልግ አብቃይ በሆኑ አካባቢዎች በድጋሚ በተቀሰቀሰው የዝናብ እጥረት ምክንያት ከአምስት ሚሊዮን በላይ ዜጎች ለዕለት ደራሽ አስቸኳይ ዕርዳታ መዳረጋቸው ሲዘገብ ሰንብቷል፡፡

በበልግ ወቅት የሚጠበቀው የዝናብ ስርጭት መቀነሱም በበልግ ዝናብ አምራች የሆኑ አካባቢዎች የምርት መቀነስ እንደሚጠብቃቸው በመገመቱ፣ በድርቅ የተመቱትን አካባቢዎች ይበልጥ ሥጋት ውስጥ እንደከተታቸው ሪፖርቶች ይፋ አድርገዋል፡፡ በዚህ ሳቢያም በድርቅ የተመቱ የአርብቶ አደር አካባቢዎች የማገገም ተስፋቸውን ጥያቄ ውስጥ እንደከተተው የብሔራዊ ሚትዮሮሎጂ ትንበያዎች ዋቢ እየተደረጉ ነው፡፡ 

በበልግ ዝናብ በመታገዝ ከሚያመርቱ አካባቢዎች መካከል የደቡብና የደቡብ ምሥራቅ ኢትዮጵያ ክፍሎች በአብዛኛውም የደቡብ ሶማሌ ክልል፣ በኦሮሚያ የቦረና ቆላማ አካባቢዎች፣ የጉጂና የባሌ ዞኖች እንዲሁም የደቡብና የአፋር ክልሎች እንደ አዲስ ባገረሸው ድርቅ ተጎጂ መሆናቸው ሲታወቅ፣ ከየካቲት አጋማሽ እስከ ግንቦት ወር በሚኖረው የበልግ ወቅት የሚያገኙት ዝናብ ደካማ እንደሚሆን በመገመቱ የማገገም ዕድላቸውን አሳሳቢ አድርጎታል ተብሏል፡፡

በእነዚህ አካባቢዎች እንደሚኖር የሚጠበቀው ደካማ የዝናብ ሥርጭት ከሚጠበቀው ከመደበኛውም ዝናብ ያነሰ እንደሚሆን በመገመቱ፣ ለበልግ ሰብሎች ታስቦ የሚደረገውን የመሬት ዝግጅትም ሆነ የሰብል መዝራት ተግባር በእጅጉ እንደሚጎዳው ይጠበቃል፡፡ የውኃ አቅርቦትንና እርጥበትን በመቀነስ በሚሳድረው ተፅዕኖ ሳቢያም ዜጎች ለምግብ እጥረትና ለተመጣጠነ ምግብ እጦት እንዲዳረጉ በር የሚከፍት በመሆኑ፣ ቀድሞውንም በድርቅ የተጎዱትን ይበልጥ ጉዳት ላይ እንደሚጥላቸው ሥጋት  ፈጥሯል፡፡

የበልግ አብቃይ የሆኑት አካባቢዎች ከ30 እስከ 60 ከመቶ የሰብል ምርታቸውን በበልግ ዝናብ አማካይነት የሚያገኙ በመሆኑ፣ የዝናቡ መምጣት በተስፋ ሲጠበቅ ቆይቷል፡፡ ይሁንና ብሔራዊ ሚቲዮሮሎጂ ይፋ ባደረገው ትንበያ መሠረት የበልግ ዝናብ ዝቅተኛ ስለሚሆን፣ በአጭር ጊዜ የሚደርሱ ሰብሎች በመዝራት በሰዎች ህልውና ላይ ጉዳት ከመድረሱ በፊት መከላከል እንደሚገባ አስጠንቅቋል፡፡ ደረቃማነትን የሚቋቋሙ ሰብሎችን መዝራት፣ የዝናብ ውኃን ማቆር፣ ዕጥርበትን ማቆየት የሚቻልባቸው ዘዴዎች እንዲተገበሩም ኤጀንሲው  አሳስቧል፡፡

የአሜሪካ ግብርና መሥሪያ ቤትን መረጃዎች የሚያጣቅሱ ሪፖርቶች እንደሚያሳዩት፣ አዲሱ የኢትዮጵያ ድርቅ 5.6 ሚሊዮኖችን ለአስቸኳይ የምግብ ዕርዳታ እንደሚያጋልጣቸው ይታመናል፡፡ ብሔራዊ የሥጋት ሥራ አመራር ኮሚሽን የሚያስተባብራቸው 30 ያህል የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ኤጀንሲዎችና ሌሎች ዓለም አቀፍ የተራድኦ ድርጅቶች የሚሳተፉበት ጥምረት፣  በጥር ወር መጀመሪያ አካባቢ ይፋ ባደረጉት ሰነድ መሠረት ለድርቁ መቋቋሚ ከ948 ሚሊዮን ዶላር ያስፈልጋል፡፡ የሰብዓዊ ጉዳዮችና አስቸኳይ ዕርዳታዎች አስተባባሪ የተመድ ምክትል ዋና ፀሐፊ ስቴፈን ኦብራየን ይህንኑ በማስመልከት፣ በጥር ወር ኢትዮጵያን ለሦስት ቀናት በጎበኙበት ወቅት አስቸኳይ ዕርዳታ ለኢትዮጵያ መደረግ እንዳለበት ለዓለም አቀፉ ማኅበረሰብ ጥሪ ማቅረባቸው ይታወሳል፡፡

ዓርብ ጥር 26 ቀን 2009 ዓ.ም. ለመገናኛ ብዙኅን መግለጫ የሰጡት የመንግሥት ኮሙዩኒኬሽን ጉዳዮች ሚኒስትር ዶ/ር ነገሬ ሌንጮ፣ ለ5.6 ሚሊዮን ዜጎች ያስፈልጋል የተባለውን የ948 ሚሊዮን ዶላር ዕርዳታ በሚፈለገው መጠን ማግኘት እንዳልተቻለ መግለጻቸው ይታወሳል፡፡

 

 

 

Standard (Image)

Viewing all articles
Browse latest Browse all 720

Trending Articles