Quantcast
Channel: አስተያየት
Viewing all articles
Browse latest Browse all 720

በመድን ገበያው ፉክክር ያሽቆለቆለውን የዓረቦን ምጣኔ የሚቆጣጠር መመሪያ እየተጠበቀ ነው

$
0
0

 

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ እያሽቆለቆለ የመጣውን የመድን ኩባንያዎች የዓረቦን ምጣኔና አንዳንድ አሠራሮችን ያስተካክላል የተባለ መመሪያ ለማውጣት መዘጋጀቱ ተሰማ፡፡

የሪፖርተር ምንጮች እንደገለጹት፣ በአሁኑ ወቅት በኢንዱስትሪው እንቅስቃሴ በተለይ የዓርቦን ምጣኔ በየጊዜው እያየለ በመጣው ከፍተኛ ፉክክር ሳቢያ እያሽቆለቆለ በመሆኑና በአገሪቱ መድን ኢንዱስትሪ ውስጥ አሉታዊ ተፅዕኖ በማሳደሩ፣ ይህንን ችግር ለማስተካከል ያስቻላል የተባለ ብሔራዊ ባንክ ይፋ እንደሚያደርግ እየተጠበቀ ነው፡፡

ጥቂት የመድን ሽፋን የሚሰጥባቸው አገልግሎቶች ዋጋቸው (ዓርቦን) ላይ ያለውን ማሽቆልቆል ለመግታትና ለማስተካከል፣ የችግሩን ምንጭም ለማየት የሚያስችል ጥናት በሁሉም የኢንሹራንስ ኩባንያዎች ላይ ለማድረግ የኢትዮጵያ የኢንሹራንስ ኩባንያዎች ማኅበርም ይህንን ጥናት እንዲያቀርብ እየሠራ እንደሚገኝ ታውቋል፡፡

ጥናቱ ብሔራዊ ባንክ እንደሚያወጣው ለሚጠብቀው መመሪያ ግብዓት እንዲሆን ታስቦ የሚካሔድ ሲሆን፣ ማኅበሩ ጥናቱን እንዳጠናቀቀ ለብሔራዊ ባንክ እንደሚያቀርበውም ታውቋል፡፡ የዓርቦን ምጣኔ ላይ የሚታየውን ችግር ለመፍታት ብሔራዊ ባንክም እንቅስቃሴ እያደረገ ስለመሆኑ የሚጠቅሱት ምንጮች፣ በየጊዜው እያሽቆለቆለ የመጣው የዓረቦን ምጣኔ መድን ድርጅቶችን ሳያከስር እንዲሁም አደጋ ሳያስከትል ለመግታት እንደሚያስችል ይታመናል፡፡

እንደ ምንጮች ገለጻ፣ ብሔራዊ ባንክ እንደሚያወጣ ከሚጠበቀው መመሪያ ጎን ለጎን፣ በዓርቦን ተመን አሠጣጥ ላይ ተጨማሪ ዕርምጃዎችም ይፋ ሊደረጉ እንደሚችሉ ኩባንያዎቹ በመጠባበቅ ላይ ይገኛሉ፡፡

በአብዛኛው በተሽከርካሪ የመድን ሽፋን ላይ ያደላው የአገሪቱ መድን አሰጣጥ፣ የዓርቦን ምጣኔው እያሽቆለቆለ በመምጣቱ በአገሪቱ የኢንሹራንስ ኩባንያዎች ገቢና ዓመታዊ ትርፍ ላይ አሉታዊ ተፅዕኖ እየፈጠረ ይገኛል፡፡ ባልተገባ ውድድር ኢንዱስትሪው እየተጎዳ ስለመሆኑም የሚገልጹ አሉ፡፡ በኢንዱስትሪው ውስጥ 17 ሲኖሩ፣ የኢንሹራንስ ኩባንያዎቹ በገበያው ላይ ተፅዕኖ እያሳረፈ ያለውን የዓርቦን ተመን ለማስተካከል ጥረት እንዲደረግና ጥናት ቀርቦ ዕርምጃ እንዲወስድ በጋራ መወሰናቸውም ታውቋል፡፡

በአሁኑ ወቅት የተወሰኑ የግል መድን ኩባንያዎች ኢንዱስትሪው የሚታየውን የገበያ መቀዛቀዝ በመንተራስ መፍትሔ ለማግኘት ከፍተኛ ባለአክስዮኖችን በመጥራት መምከር እንደጀመሩም ለማወቅ ተችሏል፡፡

ለገበያው መቀዛቀዝ ምክንያት ከሚደረጉት አንዱ የዓርቦን ተመን ምጣኔ ሲሆን በቅርቡ የወጣ ጥናት እንደሚያሳየውም የዓርቦን ዋጋ በየጊዜው ማሽቆልቆሉ ሳያንስ፣ እንደ ተሽከርካሪ መለዋወጫ ያሉ ዕቃዎች ዋጋ መናሩም ለኢንዱስትሪው ፈተና ሆኗል፡፡ በዚሁ ጥናት መሠረት ሞተር ነክ የሆኑ የኢንሹራንስ ሽፋኖች ላይ ጎልቶ ታይቷል፡፡

ባለፉት 20 ዓመታት ውስጥ 17 ኩባንያዎችን ያፈራው የኢትዮጵያ መድን ኢንዱስትሪ፣ ሁሉም ኩባንያዎች ተደምረው ያስመዘገቡት ዓመታዊ ትርፍ አንድ ቢሊዮን ብር ላለማስመዝገቡ አንዱ ማሳያ ይኸው የዓርቦን ምጣኔ እየቀነሰ መምጣቱ ነው፡፡ ከአሥር ዓመት በፊት ለአንድ ፈሳሽ ማመላለሻ ተሽካርካሪ የመድን ሽፋን እንዲያገኝ የሚከፈለው ዓረቦን የመኪናው ጠቅላላ ዋጋ በ3.75 በመቶ ተባዝቶ ነበር፡፡ አሁን ግን ዋጋው ከዕጥፍ በላይ ቀንሶ እስከ 1.5 በመቶ ባለው ተመን እየተባዛ በሚገኝ የስሌት ዋጋ መሠረት ሽፋን እየተሰጠበ በመሆኑ፣ ለዓረቦን የሚከፈለው ዋጋ በእጅጉ እየቀሰነ ለመምጣቱ አስረጅ ሆኗል፡፡

ለግል ተሽከርካሪዎችም ቢሆን ከአሥር ዓመት በፊት የዓርቦን መጠኑ የመኪናው ዋጋ በ1.5 በመቶ የሚባዛ ነበር፡፡ አሁን ግን ይህ መጠን ከአንድ በመቶ በታች ወርዷል፡፡ የአብዛኞቹ የተሽከርካሪ መድን የዓረቦን ዋጋ ባለፉት አሥር ዓመታት ውስጥ እያሽቆለቆለ ቢመጣም በአንፃሩ ግን ከፍተኛ የመድን ካሳ ክፍያ እየተጠየቀበት የሚገኘው ይኸው የተሽከርካሪዎች ኢንሹራንስ መሆኑ ደግሞ ክስተቱን እንቆቅልሽ አድርጎታል፡፡ 

Standard (Image)

Viewing all articles
Browse latest Browse all 720

Trending Articles