Quantcast
Channel: አስተያየት
Viewing all articles
Browse latest Browse all 720

የንግድ ምክር ቤት አጣሪ ግብረ ኃይል በመጪው ጥር ወር ምርጫ እንዲካሄድ ውሳኔ አሳለፈ

$
0
0

የኢትዮጵያ ንግድና ዘርፍ ማኅበራት ምክር ቤት ስምንተኛ ጠቅላላ ጉባዔውን ለማካሄድ ችግር እንዳጋጠመው በመግለጹ ምክንያት ችግሩን ለመፍታትና ተፈጠሩ የተባሉትን አለመግባባቶች ለመቅረፍ የተቋቋመው አጣሪ ግብረ ኃይል ሪፖርቱን ይፋ አደረገ፡፡ ስምንተኛ ጠቅላላ ጉባዔውን ለማካሄድ ያስችላሉ ተብለው በግብረ ኃይሉ የቀረቡትን የውሳኔ ሐሳቦችም 18ቱ አባል የንግድና ዘርፍ ማኅበራት ምክር ቤቶች ረጅም ጊዜ ከፈጀ ክርክር በኋላ በመቀበላቸው ተፈጻሚ እንዲሆኑ ከስምምነት ላይ ደርሰዋል፡፡

አጣሪ ግብረ ኃይሉ ሰኞ፣ ታኅሳስ 24 ቀን 2009 ዓ.ም. ይፋ ባደረገው ሪፖርት ላይ የመከሩት 18ቱ አባል ምክር ቤቶች፣ የአገር አቀፉን ንግድ ምክር ቤት ስምንተኛ ጠቅላላ ጉባዔን ማካሄድ ያስቻላል በማለት ግብረ ኃይሉ ባቀረበው ሐሳብ መሠረት ጠቅላላ ጉባዔውና ምርጫው ጥር 30 ቀን 2009 ዓ.ም. እንዲካሄድ ተስማምተዋል፡፡

የአገር አቀፉ የንግድና የዘርፍ ማኅበራት ምክር ቤት ጠቅላላ ጉባዔና ምርጫ የሚካሄደው ግን በግብረ ኃይሉ ውሳኔ መሠረት ተጨማሪ ማጣራት ተደርጎ ከሚገኘው ውጤት በመነሳት ተጨማሪ ውሳኔ ተካቶበት እንደሆነ ታውቋል፡፡ ግብረ ኃይሉ ለውሳኔ ካቀረባቸውና ስምምነት ላይ ከተደረሰባቸው አንኳር ጉዳዮች መካከል 18ቱ አባል ምክር ቤቶች እያንዳንዳቸው በሁለት አባላት እንዲወከሉ በማድረግ ምርጫው እንደሚካሄድ የተባለው የስምምነቶቹ አንዱ አካል መሆኑን የግብረ ኃይሉ ሰበሳቢ አቶ አሰፋ ገብረሥላሴ አስታውቀዋል፡፡  

ግብረ ኃይሉ ያቀረባቸው የውሳኔ ሐሳቦች ሙሉ ቀን ሲያከራክሩ ቢውሉም፣ ሁለት ጉዳዮች ብቻ በድምፅ ብልጫ ውሳኔ ተሰጥቶባቸው ቀሪዎቹ የግብረ ኃይሉ ሐሳቦች ግን ተቀባይነት በማግኘታቸው ስምምነት ተደርሶባቸዋል፡፡

ከዚህ ቀደም በተካሄደው ምርጫ ወቅት በርካታ ግድፈቶችን ማግኘቱን ያረጋገጠው ግብረ ኃይሉ፣ ቀጣዩን ምርጫ ለማካሄድ ያስችላሉ ያላቸውን ጉዳዮች ብቻ ከሕግ አንፃር በመለየት እንዲፈጸሙ ማድረጉን አስታውቋል፡፡ አባል ምክር ቤቶች ከሥር ምርጫ ሳያካሂዱ ወደ ላይኛው የአመራር እርከን ላይ የወጡ አመራሮቻቸውን በሚመለከት በሕጉ መሠረት መረጃ ማቅረብ ካልቻሉ እንዲሰረዙ በማለት ውሳኔ አሳልፏል፡፡ በዚህም መሠረት እስከ ምርጫው ዋዜማ ድረስ ተጣርቶ ዕርምጃ እንዲወሰድበት ለማስቻል ኃላፊነቱን ቦርዱና ጽሕፈት ቤቱ እንዲወስዱ ተደርጓል፡፡

ሕጋዊ የምዝገባ ሰርተፍኬት የሌላቸው አባላትም እንዲሰረዙ ጭምር በማድረግ ጠቅላላ ጉባዔውን ለማካሄድ ስምምነት የተደረሰ ሲሆን፣ ሕጋዊ የምዝገባ ሰርተፍኬት ሳይኖረው ለዓመታት ሲመርጡና ሲመረጡ የነበሩ የንግድ ምክር ቤት አመራር አባላትም እንደተገኙ ግብረ ኃይሉ ባቀረው ሪፖርት ጠቅሷል፡፡ የምርጫ ሒደቱም እንደ ቀድሞው በአስመራጭ ኮሚቴ በኩል ሳይሆን በጽሕፈት ቤቱ አማካይነት እንዲካሄድ ወስኗል፡፡ ወደዚህ ውሳኔ የደረሰውም አስመራጭ ኮሚቴ ለንግድ ምክር ቤቱ ውዝግብ መባባስ ግንባር ቀደም ሚና እንደነበረው በማረጋገጡ መሆኑን ግብረ ኃይሉ አስታውቋል፡፡  የተባለው የአባልነት መዋጮ ከፍተኛ በመሆኑ እንዲቀንስ ማለት የተሻሻለው መተዳደሪያ ደንብ በድጋሚ እንዲፈተሽ የሚል ውሳኔም አሳልፏል፡፡

በዕለቱ በርካታ ክርክር ያስነሱ ጉዳዮች ቢደመጡም ጠቅላላ ጉባዔውን ለማካሄድ ሲባል ስምምነት የተደረሰባቸው ጉዳዮችን ተቀብሎ ምርጫው እንዲካሄድ ለማድረግ መግባባት ላይ ተደርሷል፡፡ የአባላት ቁጥርን በተመለከተ መረጃ አቅርቡ የተባሉ የንግድ ምክር ቤቶች ከዚህ ቀደም እንዳላቸው ባስታወቁት የአባላት ቁጥር ብዛት ልክ መረጃ ሊያቀርቡ ባለመቻላቸው፣ ያስመዘገቧቸው አባላት ቁጥር ከመተዘገበው በታች በእጁ እንዳሽቆለቆለ ለማወቅ ተችሏል፡፡

                   

Standard (Image)

Viewing all articles
Browse latest Browse all 720

Trending Articles